የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
አማርኛ
፦
  • ፡
  • መጽሐፍ ቅዱስ
  • የሕትመት ውጤቶች
  • ስብሰባዎች
አማርኛ ጽሑፎች (1991-2025)
ውጣ
ግባ
የመጠበቂያ ግንብ የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
መጠበቂያ ግንብ
የኢንተርኔት ቤተ መጻሕፍት
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • ዛሬ

ማክሰኞ፣ ሐምሌ 15

ግልገሎቼን ጠብቅ።—ዮሐ. 21:16

ሐዋርያው ጴጥሮስ ለሽማግሌዎች “የአምላክን መንጋ እንደ እረኞች ሆናችሁ ተንከባከቡ” የሚል ማበረታቻ ሰጥቷቸዋል። (1 ጴጥ. 5:1-4) ሽማግሌ ከሆንክ፣ ወንድሞችህንና እህቶችህን እንደምትወዳቸው እንዲሁም እነሱን መንከባከብ እንደምትፈልግ እርግጠኞች ነን። ይሁንና አንዳንድ ጊዜ በሥራ ከመወጠርህ ወይም ከመድከምህ የተነሳ ይህን ኃላፊነትህን መወጣት እንደማትችል ሆኖ ሊሰማህ ይችላል። ታዲያ ምን ማድረግ ትችላለህ? ስሜትህን አውጥተህ ለይሖዋ ንገረው። ጴጥሮስ እንዲህ ሲል ጽፏል፦ “የሚያገለግል ማንም ቢኖር አምላክ በሚሰጠው ኃይል ተማምኖ ያገልግል።” (1 ጴጥ. 4:11) ወንድሞችህንና እህቶችህን የሚያጋጥሟቸው አንዳንድ ችግሮች በዚህ ሥርዓት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ሊፈቱ አይችሉ ይሆናል። ይሁንና “የእረኞች አለቃ” የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ከአንተ ይበልጥ ሊረዳቸው እንደሚችል አትዘንጋ፤ በአሁኑ ጊዜም ሆነ በአዲሱ ዓለም ውስጥ ሊረዳቸው ይችላል። አምላክ ከሽማግሌዎች የሚጠብቅባቸው ወንድሞቻቸውን እንዲወዱ፣ እንደ እረኛ እንዲንከባከቧቸው እንዲሁም ‘ለመንጋው ምሳሌ እንዲሆኑ’ ብቻ ነው። w23.09 29-30 አን. 13-14

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ረቡዕ፣ ሐምሌ 16

ይሖዋ የጥበበኞች ሐሳብ ከንቱ እንደሆነ ያውቃል።—1 ቆሮ. 3:20

ከሰብዓዊ አስተሳሰብ መራቅ ይኖርብናል። ነገሮችን በሰብዓዊ ዓይን መመልከት ከጀመርን ይሖዋንና መሥፈርቶቹን ችላ ልንል እንችላለን። (1 ቆሮ. 3:19) “የዚህ ዓለም ጥበብ” በአብዛኛው ለኃጢአተኛው ሥጋችን የሚማርክ ነው። አንዳንድ የጴርጋሞንና የትያጥሮን ክርስቲያኖች በከተሞቹ በተስፋፋው ጣዖት አምልኮና የብልግና አኗኗር ተስበው ነበር። የፆታ ብልግናን በቸልታ በማለፋቸው ኢየሱስ ለሁለቱም ጉባኤዎች ጠንከር ያለ ምክር ሰጥቷቸዋል። (ራእይ 2:14, 20) በዛሬው ጊዜም የዓለምን የተሳሳተ አመለካከት እንድንቀበል ጫና ይደረግብናል። የቤተሰባችን አባላትና የምናውቃቸው ሰዎች ሊያባብሉንና አቋማችንን እንድናላላ ሊያሳምኑን ይሞክሩ ይሆናል። ለምሳሌ፣ ለምኞታችን እጅ መስጠት ምንም ችግር እንደሌለው ወይም የመጽሐፍ ቅዱስ የሥነ ምግባር መሥፈርቶች ጊዜ ያለፈባቸው እንደሆኑ ይናገሩ ይሆናል። አንዳንድ ጊዜ ደግሞ የይሖዋ መመሪያዎች በበቂ መጠን ግልጽ እንዳልሆኑ እናስብ ይሆናል። ይባስ ብሎም ‘ከተጻፈው ለማለፍ’ ልንፈተን እንችላለን።—1 ቆሮ. 4:6፤ w23.07 16 አን. 10-11

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025

ሐሙስ፣ ሐምሌ 17

እውነተኛ ወዳጅ ምንጊዜም አፍቃሪ ነው፤ ደግሞም ለመከራ ቀን የተወለደ ወንድም ነው።—ምሳሌ 17:17

የኢየሱስ እናት ማርያም ጥንካሬ አስፈልጓት ነበር። ማርያም አላገባችም፤ ሆኖም እንደምትፀንስ ተነገራት። የራሷን ልጆች አሳድጋ አታውቅም፤ ሆኖም መሲሑን ማሳደግ ሊኖርባት ነው። ደግሞም ከወንድ ጋር ግንኙነት ሳትፈጽም ስላረገዘች ሁኔታውን ለእጮኛዋ ለዮሴፍ እንዴት ልታብራራለት ትችላለች? (ሉቃስ 1:26-33) ማርያም ጥንካሬ ያገኘችው እንዴት ነው? የሌሎችን እርዳታ ለማግኘት ጥረት አድርጋለች። ለምሳሌ የተሰጣትን ኃላፊነት አስመልክቶ ተጨማሪ መረጃ እንዲሰጣት ገብርኤልን ጠይቃዋለች። (ሉቃስ 1:34) ከዚያ ብዙም ሳይቆይ ደግሞ ዘመዷን ኤልሳቤጥን ለመጠየቅ ረጅም መንገድ ተጉዛ “በተራራማው አገር” ወደምትገኝ አንዲት የይሁዳ ከተማ ሄዳለች። ኤልሳቤጥ ማርያምን አመሰገነቻት፤ እንዲሁም በይሖዋ መንፈስ ተመርታ በማርያም ማኅፀን ውስጥ ያለውን ልጅ በተመለከተ የሚያበረታታ ትንቢት ተናገረች። (ሉቃስ 1:39-45) ማርያም፣ ይሖዋ ‘በክንዱ ታላላቅ ሥራዎች እንዳከናወነ’ ገልጻለች። (ሉቃስ 1:46-51) ይሖዋ በገብርኤልና በኤልሳቤጥ አማካኝነት ማርያምን አጠንክሯታል። w23.10 14-15 አን. 10-12

ቅዱሳን መጻሕፍትን በየዕለቱ መመርመር—2025
ቤተ መጻሕፍታችንን በመጠቀምህ ደስ ብሎናል።
ይህ ቤተ መጻሕፍት የይሖዋ ምሥክሮች በተለያዩ ቋንቋዎች ያዘጋጇቸውን ጽሑፎች ተጠቅሞ ምርምር ለማድረግ ያስችላል።
የሕትመት ውጤቶችን ለማውረድ እባክህ jw.orgን ተጠቀም።
  • አማርኛ
  • አጋራ
  • የግል ምርጫዎች
  • Copyright © 2025 Watch Tower Bible and Tract Society of Pennsylvania
  • የአጠቃቀም ውል
  • ሚስጥር የመጠበቅ ፖሊሲ
  • ሚስጥር የመጠበቅ ማስተካከያ
  • JW.ORG
  • ግባ
አጋራ